ካመላ ሃሪስ ደቡብና ሰሜን ኮሪያን የሚለየውን ከወታደራዊ ኃይል ነጻ ቀጣና ይጎበኛሉ

Your browser doesn’t support HTML5

የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዝደንት ካመላ ሃሪስ ደቡብና ሰሜን ኮሪያን የሚለየውና ከወታደራዊ ሃይል ነጻ ቀጣና እንደሚጎበኙ የዋይት ሃውስ ባለስልጣናት አስታውቀዋል። በዚህም ካለፉት ሶስት ዓመታት ወዲህ ሥፍራውን በመጎብኘት ከፍተኛዋ የዩናትድ ስቴትስ ባለስልጣን ይሆናሉ፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዝደንት ካመላ ሃሪስ ደቡብና ሰሜን ኮሪያን የሚለየውና ከወታደራዊ ሃይል ነጻ ቀጣና እንደሚጎበኙ የዋይት ሃውስ ባለስልጣናት አስታውቀዋል። በዚህም ካለፉት ሶስት ዓመታት ወዲህ ሥፍራውን በመጎብኘት ከፍተኛዋ የዩናትድ ስቴትስ ባለስልጣን ይሆናሉ፡፡

ሃሪስ የሳምንቱን አብዛኛውን ቀናት በደቡብ ኮሪያና ጃፓን ይከርማሉ። የቻይና ተጽዕኖ እየተጠናከረ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የባይደን አስተዳደር ሁለቱን የምሥራቅ እሲያ ሀገሮች እንደ ቁልፍ አጋር የሚመለከታቸው መሆኑን ጠቅሰው የቪኦኤዎቹ አኒታ ፓወል ከዋይት ሃውስና ቢል ጋሎ ከቶኪዮ ተከታዩን ዘገባ አስተላልፈዋል።