"(ድሉ) ይሄ ትውልድ በተለይ በአትሌቲክሱ አደራ ያልበላ መሆኑን ያረጋገጠ ነው "፣ አቶ ተፈራ ሞላ(የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን መሪ)
Your browser doesn’t support HTML5
ኦሪገን -ዩጂን ላይ ሲደረግ በሰነበተው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ላይ ከተወዳዳሩ የዓለም ሀገራት መካከል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ፣ የዩናይትድ ስቴትስ አትሌቲክስ ቡድንን በመከተል ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል።ይሄ ድል ለስፖርቱ እና ከስፖርቱ ባሻገር ስላለው ፋይዳ ለማወቅ የአትሌቲክስ ቡድኑን መሪ አቶ ተፈራ ሞላን ጠይቀናል።