አትሌቲክስ ለማህበረሰባዊ ትስስር ፣ ቆይታ ከኤርሚያስ አየለ ጋር

Your browser doesn’t support HTML5

በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ በሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ዘንድ አትሌቲክስን በመጠቀም ትስስርን ለመፍጠር ያለመ Run in the USA የተሰኘ የ5ኪሜ የሩጫ ውድድር ተካሄዷል። በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያዊያን የስፖርት ፌዴሬሽን ዓመታዊ ፌስቲቫል መዝጊያ ቀን በነበረው ውድድር ታዳጊ ህጻናትም የ1 ማይል ውድድር አድርገዋል። ስለ ውድድሩ ፋይዳ ለማወቅ ሀብታሙ ስዩም ከውድድሩ አዘጋጆች መካከል አንዱ ከሆነው ኤርሚያስ አየለ ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል ።