"የፊታችንን ጠባሳ ነው . . .በአደባባይ ያሳየሁት" የፊልም ባለሙያ ዮሃንስ ፈለቀ

Your browser doesn’t support HTML5

ባሳለፍነው ቅዳሜ ምሽት ሜሪላንድ ግዛት ውስጥ በሚገኘው ሞንት ጎመሪ ኮሌጅ የኪነጥበባት አዳራሽ ውስጥ ፣ በዮሃንስ ፈለቀ የተዘጋጀው «ዘ ኢንስ አንድ አውትስ» የተሰኘ ዘጋቢ ፊልም ተመርቋል። አንድ ኢትዮጵያዊ ፊልም ባለሙያ በስደት በሚኖርባት ዩናይትድ ስቴትስ ህልሙን ለማሳካት የሚያልፍበትን ውጣ ውረድ የሚያስቃኘው ፊልም ፣ ለእይታ በቀረበበት ምሽት ታዋቂ ገጣሚያንን ጨምሮ ዕውቅ ኢትዮጵያዊያን ስራቸውን ለታዳሚው አቅርበዋል።