የማይነገረውን የደፈረች የፊልም ባለሞያ

Your browser doesn’t support HTML5

የማይነገረውን የደፈረች የፊልም ባለሞያ

የግራፊክስ፣ አኒሜሽን እና የፊልም ባለሞያ የሆነችው ረድኤት አባይነህ ብዙ ፍቅር የተሰኘ ፊልም ደራሲ እና ዳይሬክተርም ናት። አብዛኛውን ጊዜ ስራዎቿ በጾታ እኩልነት ላይ የሚያተኩሩ ሲሆን ብዙ ፍቅርም አንዲት ታናሽ ወንድሟ የጎረቤት ሴት ልጅ የደፈረ፣ ታላቅ እህት ወንድሟ እንዳይታሰር በምታደርገው ትግል እና በሕሊና ጥያቄዋ ዙሪያ ያተኩራል።

ረድኤት በአሁን ሰዓት ነዋሪነቷ በእንግሊዝ ሃገር ሲሆን የተለያዩ በሴቶች መብት ዙሪያ የሚያጠነጥኑ የግራፊክስ ስራዎችን ትሰራለች። ከዚህ በተጨማሪም በእንግሊዝ ሃገር በሚገኝ የአኒሜሽን ድርጅት ውስጥ የምታገለግል ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ በተጓዘችባቸው ጊዜያት ለዩንቨርስቲ ተማሪዎች በራሷ ተነሳሽነት የአኒሜሽን ስልጠናዎችን ታዘጋጃለች።

/ዝርዝሩን ከተያያይዘው የምስል ፋይል ይከታተሉ/