39ኛው የኢትዮጵያዊያን የስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ ፌስቲቫል ተጀመረ
Your browser doesn’t support HTML5
ከ30 የሚበልጡ ከሁሉም የዩናይትድ ስቴትስ ግዛቶች እንዲሁም ከከካናዳ የመጡ የትውልደ-ኢትዮጵያዊያን ቡድኖች በስፖርት ደንብ የሚፎካከሩበት የኢትዮጵያ የስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ ፌስቲቫል በትናንትናው ዕለት ተጀመሯል። በአባቶች ቡራኬ እና መልእክት የተከፈተው ዝግጅቱ ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ህይወታቸውን በግፍ ላጡ ዜጎች የህሊና ጸሎት አፍታም ወስዷል ።
ዘንድሮ ላይ የቀድሞውን የኦሜድላ እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጨዋች ክብሮም ተወልደ መድህንና ፣ የቀድሞው የአሜሪካ ድምጽ ጋዜጣ አዲሱ አበበን የክብር እንግዶች የሆኑበት መርሀ-ግብር ፣ ሌሎች ከኢትዮጵያ የመጡ እንግዶችንም ተጋባዥ አድርጓል ።