ክረምቱ ተስፋ መሰነቁን የሚቲኦሮሎጂ ኢንስቲትዩቱ ገለፀ

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ የክረምቱ ዝናብ በበቂ መጠን እንደሚጥል የኢትዮጵያ ሚቲኦሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተንብይዋል።

በአሁኑ ወቅት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ላይ ያለው ንብረት አመቺ መሆኑንና ይህም መጭው ክረምቱ በእርጥበት መጠኑም በቆይታውም በቂ እንደሚሆን እንደሚጠቁም በኢንስቲትዩቱ ትንበያ ክፍል ባልደረባ ወይዘሮ ምህረት ሙሉነህ ለቪኦኤ ገልፀዋል።

በሌላ በኩል ዝናቡ ኦሮምያ ውስጥ በምሥራቅ ሸዋ አካባቢዎች ዘግይቶ መጀመሩ የተነገረ ሲሆን በባሌ ዞን ደግሞ እስካሁን አለመዝነቡን የአካብባቢው የግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊዎች አመልክተዋል።