“የሽብር ጥቃቶች” ሙከራዎችን ማክሸፉን አማራ ክልል አስታወቀ

Your browser doesn’t support HTML5

“በአማራ ክልል የተጀመረው የሕግ ማስከበር ዘመቻ የውጭና የውስጥ ኃይሎች ክልሉን ለማፍረስ ያቀዱትን የሽብር ተልዕኮ አክሽፏል” ሲል የክልሉ መንግሥት አስታውቋል።

የክልሉ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ በሰጡት መግለጫ “ሰሞኑን ባህር ዳር ከተማ ላይ ተሞክሮ የከሸፈው የሽብር ጥቃት በሌሎች የየክልሉ ከተሞች ውስጥም ለማድረግ ተሞክሯል” ብለዋል።

ከትናንት በስተያ ሰኞ ባህር ዳር ከተማ ላይ አራት ፍንዳታዎች መድረሳቸው የተዘገበ ሲሆን በሰውም ሆነ በንብረት ላይ ጉዳት እንዳልደረሰ ተነግሯል።