አምስት ሴት የዩንቨስቲ ተማሪዎች የወረቀት ዋጋን የሚቀንስ ግብዓት ፈጠሩ

Your browser doesn’t support HTML5

ከውጪ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የወረቀት ማምረቻ ግብዓቶች ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ማሻቀብ ወረቀትን በዋናነት የሚጠቀሙ ምርቶች ከገበያ ውጪ እንዲሆኑ አሊያውም ዋጋቸው ከእጥፍ በላይ እንዲጨምር አድርጓል። በአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩንቨርስቲ የአምስተኛ አመት ኬሚካል ምህንድስና ተማሪ የሆኑ አምስት ወጣት ሴት ተማሪዎች የአትክልት እና ፍራፍሬ ተረፈ ምርት በመጠቀም በትምህርት ቤታቸው ቤተሙከራ ባገኙት የፈጠራ ውጤት ታዲያ ግብዓቱን በሀገር ውስጥ ማምረት ችለዋል።

ከውጪ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የወረቀት ማምረቻ ግብዓቶች ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ማሻቀብ ወረቀትን በዋናነትየሚጠቀሙ ጋዜጦች ከገበያ ውጪ እንዲሆኑ አሊያውም ዋጋቸው ከእጥፍ በላይ እንዲጨምር አድርጓል። መፅሃፍትምእንዲሁ እንደልብ መታተም አልቻሉም። በአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩንቨርስቲ የአምስተኛ አመት ኬሚካልምህንድስና ተማሪ የሆኑ አምስት ወጣት ሴት ተማሪዎች የአትክልት እና ፍራፍሬ ተረፈ ምርት በመጠቀም በትምህርትቤታቸው ቤተሙከራ ባገኙት የፈጠራ ውጤት ታዲያ ግብዓቱን በሀገር ውስጥ ማምረት የቻሉ ሲሆን ሲሆን ሀገሪቱንየውጭ ምንዛሬን በማስቀረት እና አካባቢን በመጠበቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል። ስመኝሽ የቆየ ከተማሪዎቹ ሶስቱንበፈጠራ ስራቸው ዙሪያ አናግራቸዋለች፣ በቅድሚያ ራስቸውን በማስተዋወቅ ይጀምራሉ።