ግብርናን ለማዘመን ስላለመው "ለእርሻ " አገልግሎት ጥቂት ነገሮች

Your browser doesn’t support HTML5

ከህዝቧ መካከል አብዛኛው በግብርና መስክ በተሰማራባት ኢትዮጵያ ፣ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን ያለሙ የተለያዩ አገልግሎቶች እየተበራከቱ ይገኛሉ። "ለእርሻ" የተሰኘው በግሪን አግሮ ሶሉሽን ተቋም የተገነባው አገልግሎት አንዱ ነው። ገበሬዎች ለእርሻ የሚፈልጓቸውን ግብዓቶችን የሚያዝዙበት፣ ሙያዊ ምክር የሚያገኙበት አገልግሎት ነው። በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣት እና አንጋፋ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ስለመሆኑ ስለ ተነገረለት አገልግሎት የበለጠ ለማወቅ ሀብታሙ ስዩም ፣የተቋሙን ኃላፊ አቶ አብርሃም እንድሪያስን በስልክ መስመር አግኝቷቸዋል። አገልግሎቱን ለመጀመር ያበቁ ምክንያቶችን ቀድሞ ያስረዳሉ።