በኢትዮጵያ በሺሆች የሚቆጠሩ ስደተኞች በግጭት ምክንያት አጣብቂኝ ውስጥ ገብተዋል

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ በሺሆች የሚቆጠሩ ስደተኞች በግጭት ምክንያት አጣብቂኝ ውስጥ ገብተዋል

በአፍሪካ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ስደተኞችን ከሚያስጠልሉ ሀገራት አንዷ በሆነችው ኢትዮጵያ ከአንድ ዓመት በላይ ለሚሆን ግዜ በዘለቁ ግጭቶች ምክንያት በትግራይ፣ በአፋር እና ቤኒሻንጉል ክልሎች ተጠልለው የነበሩ ኤርትራዊ፣ ደቡብ ሱዳናዊ እና ሱዳናዊ ስደተኞች ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች መርጃ ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ ዶክተር ማማዱ ባልዴ ለአሜሪካ ድምፅ አስታውቀዋል።

በከተማ የሚገኙ ስደተኞች ቁጥርም በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሮ 70 ሺህ መድረሱን የገለፁት ዶክተር ባልዴ ተቋሙ ስደተኞችን እና የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ለመርዳት ከጠየቀው የገንዘብ ድጋፍ 19 ከመቶውን ብቻ ማግኘቱ የሰብዓዊ ርዳታ ጥረቱን አዳጋች እንዳደረገውም አስረድተዋል።

/ሙሉ ዘገባውን ከተያይዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ/