የመረጃ ንግድ፣ ከኢንተርኔት ጋር በተቆራረጠችው መቀሌ

Your browser doesn’t support HTML5

በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ወዲህ በመቀሌ እና አከባቢዋ የኢንተርኔትና ስልክ አገልግሎት በመቋረጡ ፣ የተፈጠረውን የመረጃ ክፍተት ለመሙላት በከተማዋ ሮማናት አደባባይ ላፕቶፕ እና ተንቀሳቃሽ ስልኮችን በመያዝ የማህበራዊ ሚዲያ ስክሪን ቅጂ እና በኢንተርኔት የሚተላለፉ የመገናኛ ብዙን ቪዲዮች በመሸጥ የሚተዳደሩ ወጣቶች ብቅ ብለዋል። በአብዛኛው ስለፖለቲካ እና ስለጦርነቱ ከፌስቡክ እና ከዩቲዩብ የሚገኙት መረጃዎች እስከ አስር ብር እንደሚሸጡ ወጣቶቹ ገልፀዋል።

በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ወዲህ በመቀሌ እና አከባቢዋ የኢንተርኔትና ስልክ አገልግሎት በመቋረጡ ፣ የተፈጠረውን የመረጃ ክፍተት ለመሙላት በከተማዋ ሮማናት አደባባይ ላፕቶፕ እና ተንቀሳቃሽ ስልኮችን በመያዝ የማህበራዊ ሚዲያ ስክሪን ቅጂ እና በኢንተርኔት የሚተላለፉ የመገናኛ ብዙን ቪዲዮች በመሸጥ የሚተዳደሩ ወጣቶች ብቅ ብለዋል። በአብዛኛው ስለፖለቲካ እና ስለጦርነቱ ከፌስቡክ እና ከዩቲዩብ የሚገኙት መረጃዎች እስከ አስር ብር እንደሚሸጡ ወጣቶቹ ገልፀዋል።

በተለምዶ የቪዲዮ ቤት ተብለው የሚታወቁት እና ወጣቶች ፊልም ያዩባቸው የነበሩ ቦታዎችም አሁን ወጣቶች ተሰብስበው በማህበራዊ ሚዲያ የሚለቀቁ የፖለቲካ ትንታኔዎችን የሚሰሙበት ስፍራ ሆኗል።