የኢትዮጵያ ሙስሊም ማኅበረሰብ አባላት ተቃውሞ በዋሽንግተን ዲሲ

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያ ሙስሊም ማኅበረሰብ አባላት በጎንደር ከተማ በእስልምና ዕምነት ተከታዮች ላይ እየደረሰ ነው ያሉት የሰብዓዊ መብት ረገጣ እንዲቆም የሚጠይቅ ሰልፍ አካሂደዋል። ከኢትዮጵያ ኤምባሲ ፊት ለፊት የተለያዩ መፈክሮችን በማንገብ የተገኙት መጠነኛ ቁጥር ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በጥቃቱ ለተጎዱ ወገኖች ፍትህ እንዲሰጥ ካሳም እንዲከፈል ጠይቀዋል። ጥፋተኞቹ ወደ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ፣ ጎንደር ወደ ምትታወቅበት የመከባበር አውድ እንድትመለስ ያላቸውን ጽኑ ፍላጎትም አሳይተዋል። /ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/