በርሃሌ መጠለያ ውስጥ አምስት ስደተኞች መገደላቸውን ተመድ አስታወቀ

Your browser doesn’t support HTML5

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኛ ጉዳዮች ከፍተኛ ኮሚሽነር /ዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር/ አርብ የካቲት 11/2014 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አፋር ክልል በርሃሌ ውስጥ በሚገኘው የስደተኞች መጠለያ ካምፕ ውስጥ በደረሰ ጥቃት አምስት ሰዎች መገደላቸውና በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ደግሞ አካባቢውን ጥለው መሰደዳቸው ሪፖርት እንደደረሰው አስታውቋል።