የአፍሪካ ሕብረት መሪዎች ስለ አህጉሪቱ ደህንነት ተወያይተዋል

Your browser doesn’t support HTML5

የሽብርተኝነት እና ኢ-ሕገ መንግስታዊ የመንግስት ለውጥ መበራከት ወቅታዊ የአፍሪካ ደህንነት ዋነኛ ፈተናዎች መሆናቸውን የህብረቱ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የሕብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት በ35ኛው የመሪዎች ጉባዔ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር የአህጉሪቱን የሰላም እና ጸጥታ ችግሮች ለመቅረፍ አዲስ መንገድ መከተል አለብን ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ባደረጉት ንግግር ደግሞ፣ በኢትዮጵያ ሰላምን ለማስፈን ስለሚደረገው ጥረት ያብራሩ ሲሆን፣ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ያለን ቁርጠኝነት ፈጣን በሆነ መልኩ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ /ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ/