በሁቲ አማጺያን የተያዙት ኢትዮጵያዊ መርከበኛ ቤተሰቦች የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ድጋፍ ጠየቁ

Your browser doesn’t support HTML5

ከቀናት በፊት በየመን አማጺያኑ እጅ ከወደቁት መርከበኞች መካከል አንዱ እንደሆኑ የተነገረላቸው ኢትዮጵያዊ ቤተሰቦች ፣ የደህነነት ሁኔታቸውን ለማወቅ መቸገራቸውን ለአሜሪካ ድምጽ ተናገሩ። “ሩዋቢ” በተሰኘው መርከብ ላይ በመሃንዲስነት እያገለገሉ የነበሩት አቶ አየናቸው መኮነን ነጻነታቸውን ዳግም ያገኙ የኢትዮጵያ መንግስት እና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲያግዟቸው ቤተሰቦቻቸው ጠይቀዋል ።