የደቡብ ሱዳይ ሙርሌ አባላት ጋምቤላ ውስጥ ሰው ገደሉ

Your browser doesn’t support HTML5

ከደቡብ ሱዳን ድንበር አቋርጠው ጋምቤላ የገቡ የሙርሌ ታጣቂዎች የአካባቢውን ስምንት ሰዎች መግደላቸውንና አምስት ማቁሰላቸውን የክልሉ ፖሊስ አስታውቋል።
ታጣቂዎቹ በኙዌር ዞን አኮቦ ወረዳ ውስጥ በነዋሪዎች ላይ ፈፅመዋል ያሉትን ጥቃት ማድረሳቸውን የገለፁት የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ ባለፈው ሳምንትም ሁለት ሕፃናትን ጠልፈው መውሰዳቸውን ከሰባ በላይ ራስ የቀንድ ከብት መዝረፋቸውንም ተናግረዋል።
የክልሉ ልዩ ኃይልና ሚሊሽያ በአካባቢው ፀጥታ የማስከበር ሥራ እያከናወኑ መሆናቸውን ነገር ግን ተጨማሪ ትኩረት እንደሚያስፈልግ ኮሚሽነሩ ገልፀዋል።