የመድኃኒት እጥረት መከሰቱን ተገልጋዮች ገለፁ

Your browser doesn’t support HTML5

በመድኃኒት አቅርቦት እጥረት መቸገራቸውን ቤተሰቦቻቸውን በመንግሥት የጤና ተቋማት ውስጥ በማሳከም ላይ የሚገኙ ተገልጋዮች ቅሬታቸውን አሰሙ።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዲሬክተር ዶ/ር አብድልቃድር ገልገሎ፤ እጥረቱ የተከሰተው የአገር ውስጥ መድኃኒት አቅራቢዎች ባለማቅረባቸውና የአቅርቦት ሰንሰለቱንና ከውጭ መድሃኒት የማስገባቱ ሂደት በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክኒያት እክል ስለገጠመው ነው ብለዋል።

በአገሩቱ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ቀጥተኛ ተጎጂ ለሆኑ እና ለተፈናቀሉ ዜጎች መድሃኒት እና የጤና ቁሳቁስ እያቀረቡ በመሆናቸውም በመደበኛው ሥራችን ላይ ጫና እንዳሳደረባቸው ገልፀዋል።