ኮልን ፓወል ከፍተኛው ጀኔራል ከፍተኛው ዲፕሎማት!

Your browser doesn’t support HTML5

ኮልን ፓወል የመጀመሪያው ጥቁር የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ከፍተኛው የጦር መሪ ነበሩ፡፡ ትናንት ሰኞ፣ በ84 ዓመታቸው፣ በኮቪድ 19 ሳቢያ በተወሳሰበ የጤንነት ችግር፣ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

አሳዛኙን የኮልን ፓወል ሞት በፌስ ቡክ ያረዱት ቤተሰቦቻቸው “እጅግ ተወዳጅ የሆነውን ባል፣ አባት፣ አያትና ትልቅ አሜሪካዊ አጥተናል፡፡” ብለዋል፡፡

የቀድሞ ፕሬዚዳንቶችን ጨምሮ የዩናዩትድ ስቴትስ ከፍተኛ ባለሥልጣናትና አሜሪካውያን ሀዘናቸውን በመግለጽ ላይ ይገኛሉ፡፡