ህወሃት በተቆጣጠራቸው የአማራ ክልል ከተሞች ሰዎች ለረሀብና መደፈር መጋለጣቸውን ተፈናቃዮች ገለጹ

Your browser doesn’t support HTML5

በሰሜን ኢትዮጵያ እየተባባሰ በሄደው ግጭት ከአማራ ክልል የሚፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መሄዱንና መጠለያዎችም ከአቅማቸው በላይ ሰዎች መያዛቸውን የአካባቢው ባለሥልጣናት ለሮይተርስ ገለፁ።

እንዲሁም ህወሃት በተቆጣጠራቸው የአማራ አካባቢዎች የምግብ እጥረት ለሞት እየዳረገ መሆኑንና ሴቶችም የመደፈር ጥቃት እንደደረሰባቸው፤ ጥቃቱን ሸሽተው መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ ተፈናቃዮች ለሮይተርስ የዜና ወኪል ተናግረዋል።