መንግሥት የሚመሰርተው ብልጽግና ፓርቲ ለኢዜማ የሚሰጣቸውን ሹመቶች ላይቀበል እንደሚችል ፓርቲው ገለጸ

Your browser doesn’t support HTML5

ትናንት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዲስ መንግስት ሲመሰረት ከንቲባ ሆነው የተመረጡት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በካቢኔያቸው የኢዜማ እና የአብን አባላትን አካተዋል፡፡
የኢዜማው አቶ ግርማ ሰይፉ የኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ሆነው የተሾሙ ሲሆን፣ በጉዳዩ ላይ ለአሜሪካ ድምጽ አስተያየታቸውን የሰጡት የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ናትናኤል ፈለቀ፣ የአቶ ግርማም ይሁን የሌሎች የፓርቲው አባላት ሹመት ተቀባይነት የሚያገኘው በጠቅላላ ጉባዔው ውሳኔ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የአብን ፓርቲው አቶ የሱፍ ኢብራሂም ደግሞ የመንግስት ንብረት አስተዳደር ኃላፊ ሆነው የተሾሙ ሲሆን፣ የፌዴራል መንግስቱን ጨምሮ አጠቃላይ የመንግስት ምስረታው ሳያልቅ አቋሙን እንደማያሳውቅ ፓርቲው ገልጿል፡፡