ለመስከረም ሃያው ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ተጀመረ

Your browser doesn’t support HTML5

ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በሶማሌና ሐረሪ ክልሎች፣ እንዲሁም በደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል የምዕራብ ኦሞ ዞን መስከረም 20 ለሚካሄደው ምርጫ የመራጮች ምዝገባ መጀመሩን አስታወቀ።
በመስከረም ሃያው ምርጫ አብዛኛው መራጭና ተወዳዳሪ በሚገኝበት የሶማሌ ክልል የሚወዳደረው ኢዜማ በምርጫ ቦርድ ላይ ያሉትን ቅሬታዎች አቅርቧል። ፓርቲው ባቀረበው አቤቱታ አስቀድሞ የተበተኑ የምርጫ ካርዶችን ዋጋ ለማሳታት አዲስ የምርጫ ካርድ እንዲታተም፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ገለልተኝነታቸው እንዲረጋገጥ፣ ሁለት ተጨማሪ ምርጫ ጣቢያዎች እንዲጨመሩ የሚሉና ባጠቃላይ 8 ቅሬታዎችን አቅርቧል። ምርጫ ቦርድ ቅሬታዎቹ አስቀድመው እንዳልደረሱት አስታውቋል።