የቲያትር 100ኛ ዓመት በጎንደር ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሲዘከር

Your browser doesn’t support HTML5

በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ የጎንደር ዩኒቨርስቲ የቲያትር ጥበባት ክፍል ዘመናዊ ቲያትር በኢትዮጵያ የተጀምረበትን መቶኛ ዓመት በማሰብ ለሁለት ቀናት የቆየ መርሃግብር አካሂዷል፡፡ መርሃግብሩን የወልቂጤ፣ ደብረማርቆስ እና የወሎ ዩኒቨርስቲ የቲያትር ጥበብ ክፍሎችም የተሳተፉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ የዘመናዊ ቲያትር ጅማሮን አስታኮ በመላው ሃገሪቱ የቲያትር ጥበብ እንዲነቃቃ እና እንዲያድግ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ስለቲያትር ቡድን አባላትም በቦታው ተገኝተው ውይይቱን ተካፍለዋል፡፡