“የኢትዮጵያን ህልውና ለማስጠበቅ የሚደረገውን ሃገራዊ ጥሪ በመቀበል አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርጋለን” - የኦሮምያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት

Your browser doesn’t support HTML5

“የኢትዮጵያን ህልውና ለማስጠበቅ የሚደረገውን ሀገራዊ ጥሪ በመቀበል አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርጋለን” ሲል የኦሮምያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ቃል አቀባዩ አቶ ጌታቸው ባልቻ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃል በሀገሪቱ የሰሜን አካባቢዎች “ህወሃት እያደረገ ነው” ያሉትን ውጊያም አውግዘዋል።