ፈንጠዝያ - አዲስ የካርቱን ስዕሎች ስብስብ መፅሐፍ

Your browser doesn’t support HTML5

በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ስላቅ እና የምፀት ይዘት ያላቸውን የካርቱን ስራዎች በማውጣት የሚታወቀው የካርቱን ስዕል ባለሙያ አለማየሁ ተፈራ ለአመታት የሰራቸውን ስራዎች አሰባስቦ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የካርቱን ስዕሎች ስብስብ የያዘ መፅሃፍ ከሰሞኑ ለገበያ አቅርቧል። ፈንጠዝያ የተሰኘው ይህ መፅሃፍ ከመቶ ሀምሳ በላይ በሆኑ ገፆቹ ወቅታዊና ነባራዊ የሆኑ የፖለቲካና ማህበራዊ ጉዳዮችን የሚያነሱ የካርቱን ስራዎች የያዘ ሲሆን በተለይ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ሁኔታ የሚያሳዩ ስብስቦች እንዳሉት አለማየሁ ይናገራል። በዚህ ስራው ዙሪያ ከአለማየሁ ጋር ቆይታ ያደረገችው ስመኝሽ የቆየ ናት።