'ወጣቶችን ከሱስ ህይወት ለመታደግ በነጻ አገልግሎት የሚሰጠው ተቋም ድጋፍን ይሻል' ሲስተር ይርገዱ ሃብቴ

Your browser doesn’t support HTML5

የመጨረሻ ልጃቸው አስከፊ የሆነ የሱስ ሕይወት ገብቶ ከ10 ዓመት በላይ ከባድ ጊዜ አሳልፈዋል፡፡' ልጄ ጠፋ' ብዬ አምላኬን ብዙ ጊዜ አማርሬዋለሁ ይላሉ፡፡ ያ ቀን አልፎ ታዲያ ልጃቸው ከነበረበት ወጥቶ አሁን ጥሩ ደረጃ ላይ ደርሶላቸዋል፡፡ ይሄ የሕይወት ተሞክሯቸው ግን በሱስ የተጎዱ ወጣቶችን እየሰበቡ በማሳረፍ የጤና እና የስነ ልቦና ድጋፍ የሚያገኙበትን አዲስ ሕይወት የእጽ እና የአልክሆል እና የሱሰኝነት ህክምና ማገገሚያ ማዕከልን ወደ መመስረት መርቷቸዋል፡፡