ደደር ላይ 3.1 ንዝረት ተመዘገበ

Your browser doesn’t support HTML5

ዛሬ ማለዳ በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ደደር ከተማ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ። የመሬት መንቀጥቀጡ በድሬዳዋና ሀረር ድረስ መሰማቱን ነዋሪዎች አስታውቀዋል። ክስተቱ የአካባቢው ከተሞች በህንጻ ግንባታ ላይ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የሚያስታውስ ነው ብለዋል ባለሙያዎች።