ኮቪድ-19 በኢትዮጵያ

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ ህዝቡ ኮቪድ-19ን ለመከላከል የሚያደርገው ጥረት አናሳ ነው ሲል የጤና ሚኒስቴር ገለጸ። የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ እንዳስታወቀው፣ ለአለፉት ስድስት ወራት ለተደረጉት የዳሰሳ ጥናቶች ኮቪድ-19ን ለመከላከል የሚደረጉ ጥረቶች ዝቅተኛ ናቸው። በተለይ ት/ቤቶች ላይ 79 በመቶው የነበረው ወደ 76 በመቶው መውረዱን ጥናቱ ያሳያል ሲሉ በጤና ሚኒስቴር የኮቪድ-19 ምርምርና ጥናት ግብረ ኃይል አስተባባሪ ዶ/ር አበባየሁ ገበየሁ ተናግረዋል።