በአቤ ዶንጎሮ ጥቃት ሲቪሎች ተገደሉ

Your browser doesn’t support HTML5

በሆሮ ጉዱሩና ምስራቅ ወለጋ ዞኖች ሁለት ወረዳዎች ውስጥ ታጣቂዎች ከትናንት በስቲያ ጥቃት አድርሰው ሲቪሎችን መግደላቸው ተገለፀ። በጥቃቱ በአጠቃላይ 12 ሰዎች መገደላቸውንና ቁጥራቸው በውል ያልተገለፀ ሰዎች መቁሰላቸውን የአይን እማኝ ነን ያሉ ሰዎች ተናግረዋል። የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ በቀለ ደቻሳ "በአቤ ዶንጎሮ ወረዳ ውስጥ 'ኦነግ ሸኔ' ሶስት ሲቪሎችንና ሶስት የሚሊሻ አባላትን ገድለዋል" ብለዋል። በአፀፋውም ሁለት ታጣቂዎች ተገድለዋል ሲሉ አክለዋል።