ዳዳብ እና ካኩማ እንዲዘጋ በመወሰኑ ስደተኞች ተደናግጠዋል
Your browser doesn’t support HTML5
የኬንያ ሀገር ዉስጥ ጉዳይ በሀገሪቱ የሚገኙ ሁለቱም የስደተኞች መጠለያዎች በሁለት ሳምንታት ውስጥ እንዲዘጉ ውሳኔ አሳልፎአል። የኬንያ ሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ፍሬድ ማትያንግኢ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ተራድዖ ድርጅት ዳዳብና ካኩማ ካምፖችን እንዲዘጋ ባለፈዉ ማክሰኞ ትዕዛዝ ሰጥቷል። ስደተኞች በውሳኔው ግራ መጋባታቸዉን ሲገልጹ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከሚመለከታቸዉ ጋር ንግግር ላይ መሆኑን ገልጿል።