ታዳጊ እናቶች እና ልጆቻቸውን ከጎዳና ላይ አንስቶ እራሳቸውን እንዲችሉ የሚረዳው መሰረት በጎ አድራጎት

Your browser doesn’t support HTML5

ገና በለጋ እድሜዋ የቤተሰቧን ሕይወት ለማሻሻል ስትል ወደ ትዳር የገባቸው ወ/ሮ መሰረት አዛገ በልጅነቷ የልጅ እናት ብትሆንም ኑሮን ታግላ እራሷን አብቅታለች፡፡ ነገር ግን በለጋ እድሜ የልጅ እናት መሆን የሚያመጣውን ችግር ለመቅረፍ በጎዳና ላይ የወደቁ እናቶችን በመሰብሰብ እና መጠለያ በመስጠት የተሃድሶ መርሃግብር እንዲያገኙና በኋላም ቤት ተከራይተው እራሳቸውን ችለው እንዲወጡ ለመርዳት በመሰረት በጎ አድራጎት ድርጅት በኩል እየጣረች ነው፡፡