የኢትዮጵያ ዘመናዊ ቲያትር 100ኛ ዓመት ሊከበር ነው

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያ ውስጥ ዘመናዊ ቲያትር የተጀመረበት 100ኛ ዓመት ሊከበር መሆኑ ተበሰረ፡፡ ከጥቂት ወራት በፊት ስለቲያትር ያገባናል ባሉ አስራአንድ የቲያትር ባለሞያዎች የተመሰረተው ‘ስለቲያትር’ የተሰኘ ቡድን ከኢትዮጵያ የቲያትር ማኅበር ጋር በመተባበር ዓመቱን በሙሉ የሚዘልቅ እና በሃገሪቱ እየተዳከመ የመጣውን የቲያትር ሙያ የሚያነቃቃ መርሃግብሮችን ማቀዱን ይፋ አድርጓል፡፡ በዛሬ ዕለትም ከመገናኛ ብዙሃን ጋር የመጀመሪያውን ውይይት አድርጓል፡፡