ኢዜማ ኮንሶ ላይ ጥቃት እየደረሰብኝ ነው አለ

Your browser doesn’t support HTML5

በደቡብ ክልል የኮንሶ ዞን የኢዜማ ፓርቲ አባላት የምርጫ ቅስቀሳ በሚያደርጉበት ወቅት በፀጥታ ኃይሎች መያዛቸውን፤ ሲያዙም መደብደባቸውና መቁሰላቸውን ለሁለት ቀናት ከታሰሩ በኋላም ትናንት ማምሻውን ከእስር መለቀቃቸውን ኢዜማ ለአሜሪካ ድምፅ ገለጠ። የኮንሶ ዞን ሰላም እና ፀጥታ መምሪያ በኢዜማ ምርጫ ቅስቀሳ ምክንያት የታሰረ ሰው አለመኖሩን ጠቅሶ “መንግስት ፈርሷል” የሚል አሉባልታ በአደባባይ ሲያውጁ እና ህገ ወጥ ድርጊት ሲፈፅሙ የተያዙ ግለሰቦች መኖራቸውን ተናግሯል።