አማራ ክልል ለሚገኙ ከ250 ሺሕ በላይ ተፈናቃዮች በቂ ድጋፍ አለመድረሱን ክልሉ አስታወቀ

Your browser doesn’t support HTML5

ትግራይ ክልል ውስጥ በተካሄደው ወታደራዊ ዘመቻና ቤኒሻንጉል ጉምዝ ውስጥ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት ለተፈናቀሉ 250 ሺህ ዜጎች እስካሁን በቂ ድጋፍ አለመድረሱን የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት አስታውቋል። በሌላ በኩል በጦርነቱና በሌሎችም ጥቃቶች ለተፈናቀሉና አማራ ክልል ውስጥ ለሚገኙ ተጎጂዎች የአዲስ አበባ አስተዳደር የዕለት ደራሽ ድጋፍ ሰጥቷል።