"በኮቪድ 19 ምክንያት የተቀዛቀዘው የአካል ጉዳተኞች ስፖርት ትኩረት ያሻዋል" ጥላሁን ጀማነህ

Your browser doesn’t support HTML5

10ኛው ከተማ አቀፍ የአካል ጉዳተኞችና መስማት የተሳናቸው የስፖርት ፌስቲቫል “አካል ጉዳተኞችን ያካተተ ምቹና ዘላቂ የተሻለ ዓለምን በድህረ ኮቪድ እንገንባ” በሚል መሪ ቃል ተካሂዷል፡፡ ኤደን ገረመው በአካል ጉዳተኞች ስፖርት ክብደት በማንሳት የተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ አምስት ጊዜ ኢትዮጵያን በመወከል የተሳተፈውን አሰልጣኝ ጥላሁን ጀማነህን የዘንድሮውን ውድድር በተመለከተ አናግራው ነበር፡