የምስጋና በዓል በትልቁ የኢትዮጵያውያን ቤተሰብ

Your browser doesn’t support HTML5

በየዓመቱ የሕዳር ወር ማብቂያ የመጨረሻው ሃሙስ ዕለት በአሜሪካዊያኑ ዘንድ የሚከበረው የታንክስ ጊቪኝ ወይም የምስጋና በዓል፤ ቤተሰቦች የሚሰባሰቡበት ትልቅ በዓል ነው፡፡ ኑሯቸውን በአሜሪካ ያደርጉ ኢትዮጵያውያንም ይህንን በዓል ተስባስበው በመገናኘት ያከብሩታል፡፡ጩኒ ሙላት እና አስራ አንድ ወንድም እና እህቶቿ በየዓመቱ ይህንን ቀን፤ ከነልጆቻቸው ሰላሳ አምስት በመሆን በአንድነት ያከብሩታል፡፡ ይሁንና ዘንድሮ ግን በኮቪድ ምክንያት ይህን ማድረግ አልቻሉም፡፡