"በማሕበራዊ ሚዲያ ላይ የሚደረግ መዘላለፍ ወጣቶችን ወደ ጭንቀት እና እራስን ማጥፋት እየገፋፋ ነው"- ዛሃራ ለገሰ

Your browser doesn’t support HTML5

ዛሃራ ለገሰ የስነ ልቦና ባለሞያ እና የአስክ ዛሃራ የማሕበራዊ ሚዲያ ገጽ መስራች ናት፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ በሚታተመው እና በነጻ በሚከፋፈለው የዋትስ አፕ መጽሄት ላይም አምደኛ ነበረች፡፡ ባለፉት ጥቂት የማይባሉ ዓመታት በሙያዋ ብዙዎችን አገልግላለች፡፡ ዛሃራ ከኮቪድ 19 ወርርሽኝ ወዲህ በወር አንዴ ወጣቶችን እየጋበዘች በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ የምክር እና የውይይት አገልግሎት እየሰጠች ትገኛለች፡፡