የየመን ሁቲ አማጺያን ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ከሀገራቸው አባረሩ፣ በርካታዎችን ገደሉ

Your browser doesn’t support HTML5

የየመን ሁቲ አማጺያን በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ከሀገራቸው ለማስወጣት በከፈቱት ተኩስ በርካታ ኢትዮጵያውያን መገደላቸውን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የሆነው ሂውማን ራይትስ ዎች ትላንት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የተኩስ ጥቃቱን ለማምለጥ ወደ ሳውዲ ድምበር ለመግባት የሞከሩ በርካታ ስደተኞች ላይ የሳውዲ ድምበር ጠባቂ ወታደሮች ተኩስ በመክፈታቸው ተጨማሪ ኢትዮጵያኖች መሞታቸውንም መግለጫው አካቷል።