የመጫና ቱለማ መረዳጃና ልማት ሕዝባዊ ማኅበር ፕሬዚዳንት መደብደባቸውን ገለፁ

Your browser doesn’t support HTML5

የመጫና ቱለማ መረዳጃና ልማት ሕዝባዊ ማኅበር ፕሬዚዳንት አቶ ድርቤ ደምሴ ባለፈው ሣምንት ውስጥ መኖሪያ ቤቴ ውስጥ“በመንግሥት ፀጥታ አስከባሪዎች ተደብድቤአለሁ” ሲሉ ስሞታ አሰምተዋል።የከተማው የፀጥታና የአስተዳደር ፅህፈት ቤት ኃላፊ ስብሰባ ላይ መሆናቸውን ገልፀው ምላሽ ሊሰጡ እንደማይችሉ የተናገሩ ሲሆን ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ስለጉዳዩ መረጃ እንዳልደረሰው ገልጿል።የኦሮምያ ክልል የመንግሥት ኮምዩኒኬሽንስ ቢሮ በበኩሉ ስለጉዳዩ አጣርቶ ማብራሪያ እንደሚሰጥ አስታውቋል።