የኮሮና ወረርሽኝ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃንን ህልውና ስጋት ላይ ጥሏል

Your browser doesn’t support HTML5

የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ከጤና ባሻገር የተለያዩ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ደህንነት ላይ ጫና እያሳደረ መሆኑን ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን በወረርሽኙ ምክንያት ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ መግባቻቸውንና ከመንግስትና ሌሎች ረጂ ድርጅቶች ፈጣን ርዳታ የማያገኙ ከሆነ የተቋማቱ ህልውና ስጋት ላይ እንደሚወድቅ አስታውቀዋል። በዚህም ምክንያት ተቋማቱ ጥምረት ፈጥረው ኢንዱስትሪውን የማዳን ጥያቄ ለጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮና ለሚመለከተው አካል አቅርበዋል።