‘እነሆ ለልጆች’ - በኃይሉ ገ/እግዚአብሔር

Your browser doesn’t support HTML5

ህፃናት በስነ-ምግባር ታንፀው አድገው ነገ በሀገራዊና በራሳቸው ጉዳይ ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ ከትምህርት ቤት በቀጥታ ከሚቀስሙት ትምህርት ባሻገር፣ ከመፃህፍት፣ ፊልሞችና ከመገናኛ ብዙሃን የሚያገኟቸው መልእክቶች ትልቅ ሚና አላቸው። በተለይ ታሪክን ለልጆች በማስተማርና ማህበራዊ እሴቶችን በማስተላለፍ ረገድ ደግሞ ተረቶች ትልቅ ቦታ ይሰጣቸዋል።