በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ነፍሰጡር እናቶች የህክምና ክትትል ቀንሷል

Your browser doesn’t support HTML5

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት አብዛኛው የጤና ተቋማት የእርግዝና ጊዜአቸው ገና የሆኑትንና ተጨማሪ የጎንዮሽ ችግር የሌለባቸውን እናቶች ቀጠሮ እንዲራዘም አድርገዋል። ይህን ተከትሎ አንዳንድ ነፍሰጡር እናቶች በተሳሳተ ግንዛቤ ወደ ጤና ተቃማት ለክትትል መሄድ ፍርሀት እንዳሳደረባቸውና አንዳንዶቹም ሙሉ ለሙሉ ክትትል በማቇረጣቸው ለችግር እየተጋለጡ መሆናቸውን የህክምና ባለሙያዎች ይገልፃሉ። በዚህም ምክንያት ለተጨማሪ የጤና እክል የሚጋለጡ እናቶች ተበራክተዋል።