የኢትዮጵያ ሚዲያ ነፃነት አሁንም ከፈተና አልተላቀቀም
Your browser doesn’t support HTML5
ለረጅም አመታት ለፕሬስ ነፃነት ከሚያሰጉ አገሮች ትመደብ የነበረችው ኢትዮጵያ ላለፉት ሁለት አመታት በመገናኛ ብዙሀን እንቅስቃሴ ዙሪያ በታዩ ለውጦች ምክንያት አለም አቀፍ አድናቆት ብታገኝም በኢትዮጵያ ያለው የፕሬስ ነፃነት አሁንም ከስጋት ነፃ አይደለም። የሚዲያ ፅንፈኝነት፣ የጋዜጠኞች የሙያ ብቃት እና በነፃነት ዙሪያ የታዩት መሻሻሎች ወደኃላ የመቀልበስ ስጋት አሁንም የሚዲያው ፈተናዎች ሆነው ቀጥለዋል።