አዲሀን ከአዴፓ ጎን እንደሚቆም አስታወቀ

Your browser doesn’t support HTML5

የአማራ ክልል ገዢ ፓርቲ (አዴፓ) የህዝቡን ህልውና ለማስጠበቅ በሚደረገው ጥረት ከጎኑ እንደሚቆም ተፎካካሪው የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሀይል ንቅናቄ (አዲሀን) አስታወቀ።
አዲሀንን ጨምሮ 5 የፖለቲካ ፓርቲዎች ግንባር በመፍጠር በጋራ ለመስራት መስማማታቸውም ታውቋል። የተስማሙት ፓርቲዎችም የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሀይል ንቅናቄ የመላው አማራ አንድነት ድርጅት የመላው አማራ አንድነት ፓርቲ የአማራ ህልውና ለኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ ነፀብራቅ አማራ ፓርቲ ናቸው።