ትንሽ ድፍረት የፈጠራ ስራን እጅግ ያጎለብታል ትላለች- ፀሃፊ ተውኔት መዓዛ ወርቁ

Your browser doesn’t support HTML5

እራሴንም ሆነ በአካባቢዬ የማያቸውን ማሕበራዊ እና ኢ-ፍትሃዊ የሆኑ ነገሮች የምገልፀው በፅሁፍ ነው ትለናለች የጋቢና እንግዳችን መዓዛ ወርቁ፡፡


ከ19 ዓመት በላይ በጥብብ ወስጥ ቆይታለች፡፡ ስራዎቿ በየቤታችን ቢደርሱም እስካሁን ድረስ ግን ብዙዎቻችን አናውቃትም፡፡ ከሃያ በላይ የቴሌቭዥን እና የሬዲዮ ድራማዎችን ፅፋለች፡፡ ዝነኞቹ’ እና ከሰላምታ ጋር’ የተሰኙ ሁለት የመድርክ ቲያትሮችን ለህዝብ አድርሳለች፡፡ በተለይ ከሰላምታ ጋር በተለያዩ አገራት ከአማረኛ ቕንቕ ወጪ በሰርቢያ፣ ጀርመንኛ መጀመሪያ በተፃፈበት እንግሊዘኛ 'Deseperate to fight' ተብሎ ተተርጉሞ በብሩንዲ፣ ኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ስዊድን እና ኒውዮርክ ታይቷል፡፡ በኒዎርክ ድራማ ት/ቤት ውስጥም የምስራቅ አፍሪካ ሴት ፀሃፍት ስራዎች ውስጥ ተካቶ ለማስተማሪያነት እያገለገለ ይገኛል፡፡

በአሁን ሰዓት በከፍተኛ ጉጉት የሚታየው ደርሶ መልስ’ የቴሌቪዥን ድራማም ፀሃፊም ናት፡፡ የዛሬ የጥበብ ታዛ እንግዳች ጸሃፊ ተውኔት መዓዛ ወርቁ ናት፡፡ ከኤደን ገረመው ጋር ተከታዩን ቆይታ አድርጋለች፡፡