በሊቢያ በተፈፀመ የአየር ድብደባ 44 ሰዎች ተገደሉ

Your browser doesn’t support HTML5

ከሊቢያ ዋና ከተማ ትሪፖሊ ወጣ ብሎ በሚገኝ ታጃውራ በተባለ ፍልሰተኞች በታሰሩበት ቦታ በተፈፀመ የአየር ጥቃት እስካሁን 44 ሰዎች መሞታቸው ተረጋግጧል። 130 ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል። የተባበሩትን መንግሥታት ድርጅት ድርጊቱን በእጅጉ አውግዞታል። ጥቃቱ በደረሰበት እስር ቤት የሚገኙ ኤርትራውያን ስለ አደጋው ለአሜሪካ ድምፅ ሲናገሩ ፤ በአየር ድብደባው ሕይወታቸውን ካጡት ውስጥ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን "የሉበትም" ብለዋል።