የኪነጥበብ ሰዎች እና ጋዜጠኞች በጋራ የመናገር ነጻነትን ይዘክራሉ

Your browser doesn’t support HTML5

የዓለም የፕሬስ ነጻነት ቀንን ምክንያት በማድረግ አርብ ሚያዚያ 25/2011 በአዲስ አበባ ቲያትር እና ባህል አዳራሽ ‹‹ሳንሱር የባህል ትግል እና ነጻነት›› የተሰኘ ወይይት እና የኪነጥበብ ድግስ ተሰናድቷል፡፡

በሰላም ኢትዮጵያ የተሰናዳው ይሄ መድረክ፣ተመልካቾች በነጻ እንዲታደሙበት እንደታቀደ፣ በጋዜጠኝነቱ እና በኪነጥበቡ ዓለም የታወቁ ሰዎች እንደሚሳተፉበት አስተባባሪዎቹ ለአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ተናግረዋል፡፡

ስለ ዝግጅቱ ዓላማ እና ይዘት የዝግጅቱ አስተባባሪ የሆነውን ረዳት ፕሮፌሰር ሱራፌል ወንድሙ ከባልደረባችን ሀብታሙ ስዩም ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡