ድምጽ በጂግጂጋ የጅምላ መቃብር መኖሩ ለፖሊስ ጥቆማ ደርሶታል ኖቬምበር 17, 2018 ጽዮን ግርማ Your browser doesn’t support HTML5 በጂግጂጋ 200 ሰዎች የተቀበሩበት የጅምላ መቃብር መኖሩ ለፖሊስ ጥቆማ ደርሶታል። ፖሊስ ጥቆማውን ተቀብሎ እያጣራ መሆኑን ለፍርድ ቤት አስረድቷል። በሐምሌ ወር ከተፈፀመው ጥቃት ጋር በተያያዘ የ50 ሰዎች አስክሬን በሦስት ጉድጓድ ውስጥ ተቀብሮ መገኘቱን ፖሊስ ገልጿል። ፖሊስ በቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ መሐመድ ዑመር የመርመራ መዝገብ በጅምላ ተቀበሩ የተባሉ ከ200 በላይ ግለሰቦችን አስከሬን ለማግኘት ምርመራ እያደረኩ ነው አለ። ጽዮን ግርማ ዝርዝሩን ይዛለች።