አርቲስት ታማኝ በየነ ቅዳሜ ኢትዮጵያ ሊገባ ነው
Your browser doesn’t support HTML5
በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ተቃውሞን በማሰማት፣ ትችት በመሰንዘርና የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ጉዳይ ይዞ አደባባይ በመውጣት የሚታወቀው አርቲስት ታማኝ በየነ ከ22 ዓመታት በኋላ በመጪው ቅዳሜ ኢትዮጵያ ሊገባ መሆኑን አስታወቀ። የአርቲስት ታማኝ አቀባበል የኢትዮጵያዊያን አንድነት ማብሰሪያ ምልክት እንደሚሆን አዲስ አበባ የሚገኘው የአቀባበሉን መርሃ ግብር የሚመራው ኮሚቴ አስታውቋል።