የወልቃይት ኮሚቴ አባላትና የአብን አመራሮች ከዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት ጋር ምን ተወያዩ?

Your browser doesn’t support HTML5

የወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ ኮሚቴ አባላትና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አመራሮችና አባላት አዲስ አበባ ከሚገኙት የዩናይትድ ስቴትስ የሕዝብ እንደራሴ አባላት ጋር ተወያዩ። ለምክር ቤቱ አባላት ባለፉት 27 ዓመታት በአማራ ሕዝብ ላይ ደረሰ ያሉትን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ በደሎችና መገፍፋትን ማስረዳታቸውን አመራሮቹ ለአሚሪካ ድምፅ ተናግረዋል።